- Manufacturer: Toyota
- Model: Corolla
- Year: 1990
- Fuel: Petrol
- 1300 cc engine capacity 12 valve
- electric fuel injection
- 5 speed manual gearbox
Uncategorized
Project Manager – Job Vacancy in Ethiopia
BIYAFI Construction PLC announced the following job vacancy in Ethiopia.
Job Position: Project Manager
Vacant ID: BIY-142-20
Qualification: B.Sc. in civil engineering or related field
Minimum Experiences General / Specific: 8 years working on road construction projects 2 years as PM / construction engineering
Skill: Team work, Leadership and computer skill
Place of work: Construction site
Dead Line: 10 days
Head Office: A.A around Megenagna area
Email: Send only Application letter and CV in PDF format and corresponding credentials to biyafi.com@gmail.com
Note: Company works on cloud base platform – Employee shall be willing to work on IT technology
Articles
በጣም ገራሚ ነገር የጃልመሮ የስልክ ንግግር ወጣ
ጋዜጠኛ፡ በምዕራብ ወለጋ ስልክ የለም እንደተቋረጠ ይታወቃል፤ ያንተ ስልክ ግን ይሄው ይሰራል እያወራን ነው፤ ይሄ ነገር እንዴት ነው? አይጋጭም? አሁን ስታወራኝ ኔትወርክ አለ፤ ከየት አመጣኸው ኔትወርኩን?
ጃልመሮ፡ ጋዜጠኛ ብዙ አታናግረኝ፤ አንተ… … ኢትዮጵያ ዉስጥ የትም ቦታ ሆኔ ስራዬን ማከናወን ነው የሚጠበቅብኝ የትም ይሁን የት፡፤ አንተ ስልኬን አግኝተህ እንደደወልክልኝ ፍንፍኔ ሆኘ ስራየን ማከናወን እችላአለሁ፤ የሚከለክለኝ ሰው የለም…
ሙሉ ቃለምልልሱን ከስር ማዳመጥ ትችላላችሁ፡፡ እኔ ግን የራሴን አስተያየት ትንሽ ላክልበት፡፡ ምዕራብ ወለጋ ስልክና ኢንተርኔት መዘጋቱ የሚታወቅ ነው (ይሄንን ጉዳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ፓርላማ ላይ በይፋ ተናግረዉታል)፡፡ የሚገርመው ግን የጃልመሮ ስልክ መስራቱ ነው፡፡ እዚህ ላይ ሁለት መላ ምቶችን መገመት ይቻላል፡፡ አንደኛው ጃልመሮ እዚያው ወለጋ ስልክ ከተዘጋበት ቦታ ከጦሩ ጋር ሆኖ በልዩ የሱን ስልክ ብቻ እንዲሰራለት ተደርጎ (ይህ በቴክኖሎጅው የሚቻል ስለሆነ)፤ ሁለተኛው ሌላ ቦታ ምናልባትም እሱ እንዳለው ፍንፍኔ (አዲስ አበባ) ሆኖ ሊሆን ይችላል፡፡ ታዲያ በሁለቱም ኬዝ የመንግስት እጅ አለበት ማለት ነው፡፡ ታዲያ መንግስት ሆን ብሎ ለኦነግ ድጋፍ እያደረገ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ዉስጥ ያሉትን የኢትዮጵያ ልጆች ለምን ያስጨርሳል?
በቃለምልልሱ ላይ ጃልመሮ እንዳለው በመከላከያ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ተናግሯል፤ እንዲያዉም ጀግናው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሚባል የለም ዉሸት ነው ብሏል፡፡ እኛ ነን ጀግኖቹ ማለቱ ነው፡፡ እንዴት ከ50 ዓመት በላይ ታግሎ አንድም ድል ማግኘት ያልቻለው ኦነግ ዛሬ በድንገት እንዴት ይሄን ሁሉ ጀግንነት አገኘ? 50 ዓመት ሙሉ በትግል ላይ ሲቆይ እንዳያሸንፍ ብሎም ጭራሹን ስሙ እንኳን ሀገር ዉስጥ እንዲጠፋ ያደረገው ጀግናው መከላከያ ሰራዊት ዛሬ እንዴት በኦነግ ሊጠቃ ቻለ? እዉነት መንግስት ከኦነግ ጋር ወይስ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ነው? ሙሉ ቃለምልልሱን አድምጡትና አስተያየታችሁን ከስር ብትሰጡበት እላለሁ፡፡
Articles
በምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ ለተፈጠሩ ችግሮች ተጠያቂው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ነው
ኦነግ “በምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ ለተፈጠሩ ችግሮች ተጠያቂው የጠቅላይ ሚኒስትሩ መንግስት ነው” አለ፡፡
በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የሚመራው መንግስት በኦሮሚያ ክልል በምዕራብና ደቡብ ዞኖች እየተፈጸመ ላለው “እሮሮና ሰቆቃ” ተጠያቂ ነው ሲል የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከሰሰ።
“ይሄ ችግር በአስቸኳይ ካልተገታ በስተቀር ከዚህም ወደ ባሰ ሁኔታ አድጎ ከማንም ቁጥጥር ውጭ ሊሆን እንደሚችል ስጋታችን እየጨመረ መሆኑን በድጋሚ አስረግጠን ልንገልጽ እንወዳለን” ሲል በመግለጫው ያካተተው ኦነግ “ሆን ተብሎ በዶ/ር ዓብይ አህመድ የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት በሰላማዊ ህዝባችን ላይ እየፈጸመ ያለዉን ይህንን እሮሮና ሰቆቃ እጅግ አጥብቀን እናወግዛለን” በማለት እንዲቆም ጥሪ አቅርቧል።
መንግስት በኦሮሚያ ምዕራብ ወለጋ ዞኖች የስልክና ኢንተርኔት አገልግሎቶችን አቋርቷል ያለው ኦነግ ‘’የመንግስት ወታደሮችና ታጣቂዎች በሰላማዊ (ትጥቅ አልባ) ዜጎች ላይ እያካሄዱ ባሉት ግድያ የሰዎች ህይወት እንደ ቅጠል እየረገፈ መሆኑ” መረጃ እንደ ደረሰው የሚያትተው ጥር 23 ቀን 2012 ዓ.ም የወጣው የኦነግ መግለጫ በተለይ በምዕራብና በቄለም ወለጋ እየተፈጸመ ያለው “ግድያና ጭፍጨፋ” በቃላት መግለጽ አዳጋች ነው ብሏል፡፡ በዚህ ሳቢያም ድርጊቶቹን የሰብአዊ መብት ጥሰትና የጦር ወንጀል የሚሉ ሃረጎች ሊገልጿቸው አይችልም ሲል በመግለጫው አስታዉቋል፡፡
ስለዚህም የተጠቀሱት ችግሮች ተቀርፈው መፍትሄ ይመጣ ዘንድ “በግድያና ጭፍጨፋ በእስራትና በማንኛዉም መንገድ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በመንግስት እየተካሄደ ያለው ይሄ እሮሮና ማሰቃየት በአስቸኳይ እንዲቆም ይሄንን እያካሄዱ ያሉት የመንግስት ሃይሎች ወደ ካምፕ እንዲመለሱ፤ ያሉት ችግሮች በዉይይትና በሰላም መፍትሄ የሚያገኙበትን ሁኔታ መንግስት እንዲያመቻች፤ ከዚህ ለመሸሽ የተገደዱ ሰዎች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሮአቸዉን እንዲኖሩ፤ ከደረሰባቸው ጉዳት የሚያገግሙበት እገዛም እንዲደረግላቸው፤ እንዲሁም እየደረሰ ያለዉን ጉዳት በነጻና ገለልተኛ አካል አስፈላጊ ዓለማቀፍ ምርመራ እንዲደረግ፤” ሲል ጥሪ አቅርቧል፡፡
ይሄንን ጉዳይ በሚመለከት ሰኞ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች የቀረቡላቸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በምዕራብና በጉጅ ኦሮሚያ ዞኖች እየተካሄዱ ያሉ የመንግስት ዘመቻዎችን አረጋግጠው በጉጂ ዞን ያለው ከአካባቢው አባ ገዳዎች ጋር በተደረገ ዉይይት ቀንሷል ብለዋል፡፡ በምዕራብ ኦሮሚያ ዞኖች ደግሞ ኢንተርኔትና ስልክ መቋረጡን ገልጸው መንግስት በአካባቢው እየተደረገ ካለው ዘመቻ ጋር እንደሚገናኝና በቅርቡ መፍትሄ እንደሚያገኝም አስታዉቀዋል፡፡
በምዕራብ የኦሮሚያ ዞኖች በተለይ ክልሉ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጋር በሚያዋስንባቸው አካባቢዎች የታጠቁ ሃይሎች የሚንቀሳቀሱ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን፤ የበርካታ ዜጎችና የመንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች የሚገደሉባቸው ስፍራዎችም ናቸው፡፡ በቅርቡም ታግተዋል የተባሉ ነገር ግን መንግስት በማን፣ የት እና መቼ እንደታገቱ ሊገልጽ ያልቻለው የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጉዳይም የዚህ አካባቢ አንዱ የቅርብ ክስተት ነው፡፡
ብሩክ አብዱ
ምንጭ፡ ሪፖርተር ጥር 27 ቀን 2012 ዓ.ም
Articles
አገረ መንግስቱ በግለሰቦች እጅ ወድቆ ነበር
“አገረ መንግስቱ በግለሰቦች እጅ ወድቆ ነበር”
ጠቅልቅይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም ባደረገው ልዩ ስብሰባ ከእንደራሴዎች ለተለሱ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ በሰጡበት ወቅት የተናገሩት፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከለዉጥ በፊት ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ እንደ ሃገር መቀጠል የማትችልበት ደረጃ ላይ ደርሳ እንደነበር፤ መደበኛ ያልሆነዉና በጥቅም፣ በዝምድና እና በትዉዉቅ የተሳሰረ የመንግስት ጥልፍልፎሽ እንደነበር አስታዉሰው ይህም ከለዉጡ ማግስት የነበረዉን የመንግስትን ስራ አደጋ ላይ ጥሎት ነበር ብለዋል፡፡
ምንጭ፡ ሪፖርተር ጥር 27 ቀን 2012 ዓ.ም ገጽ 27